Friday, January 28, 2011

ዘመኑ እየተቀየረ ነው። ሳይመሽ ጥግ መያዝ ይበጃል። በቱኒዚያ፤ በግብጽ፣ በየመን የነፈሰው አቅጣጫው ወደ ኢትዮጵያ ይመስላል።

አዲስ ነገር ስላገኘን ይህችን ለማውጣት ተገደናል
 ከሳᎀኢል ሽፈራው/ዳላስ

በሰሜን አፍሪካ እየተካሄደ ላለው አዲስ የሕዝባዊ አመጽ ወገኖቻችን ጀሮ ሰጠው በሚከታተሉበት በዚህ ሰአት አንዳንድ ከነሱ ሕይወት ሌላ የሌሎች ሕይወት ምንም መስሎ የማይታያቸው ይህን አገዛዝ ለምን ወደውጭ አትመጡና አትቆጣጠሩንም። ደካሞች ናችሁ በማለት የቁጭት ምክር ሲለግሱ በዚህ ከታች በለጠፍነው ቪዲዮ ይታያል። ለሁሉም ይህን አስመልክቶ በተለየም በአካባቢያችን ነዋሪ የሆኑ ትቂት ግለሰቦች ወደአገር ጎራ ብለው ለሕወሐት/ወያኔ በውጭ በስደት ላይ የሚኖረውን ዜጋ ለምን አትቆጣጠሩትም፧ በሚል አዲስ አበባ ሸራቶን ሆቴል በተደረገ የዲያስፖራ ስብሰባ ተብሎ በተሰየመና በወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ሹማምንት በሰበሰቡት አንደኛው ሐሳብ አቅራቢ ሆነው የቀረቡት ከዚህ ከዳላስ የሔዱት ግለሰብ እንደነበሩ በተጨባጭ ማስረጃ ይቀርባል። እኒህ ግለሰብ ቤተክርስቲያን ከሰው የሌለ የመብት ጥያቄ በማቅረብ ንጹሀን ወገኖች እንዲተባበሯቸው በማድረግና ሌሎችም በተሳሳተ አሉባልታ አብረውና ተባብረው አጀንዳ ካላቸው ግለሰቦች ጋር በመሰለፋቸው ሐዘኔታችን እንደተጠበቀ ሆኖ። ይህን ዘረኛ መንግስት ለመታገል ግን ወደኋላ የማይሉት ምንም አይነት የፖሮፓጋንዳ፣ የማጥላላት ዘመቻ ቢካሄድ። ወይንም የሌለ ስም ቢሰጥና ሌላም ቢደረግ ይመስለኛል የሚደነግጥ ልቦና እንደሌለ ለግንዛቤ ይሁን።

ግለሰቦች ያሻቸውን ሊያንምኑ። ባሻቸው ድርጅት ወይንም እምነት ሊሰባሰቡ ፍጹማዊ መብት ነው። ሆኖም ስውር አጀንዳ ይዘው በሰላም በሚኖሩ ስደተኛ ወገኖች ላይ የሚያደርጉት የማጥላላት ዘመቻ ግን ሊቆም ይገባል። ወዲህ ልምጥ ወዲያ ጎበጥ የምንልም አንዱን መርጠን መሰለፍ የተሻለ የግል ክብር ነው። ክስ አቅርበው ተቋምን ከሚያንገላቱ ጋር ለመሰለፍ የከጀሉ ግለሰቦች ኢሕአፓን የግል ደካማ ጎናቸውን ማላከኪያ ሲያደርጉ ስናይ አዝነናል። ሰው ሲጣላ ኢሕአፓ ነው ። ወይንም መጠጥ ጠጥቶ መንገድ ለሳትም እነሱ ናቸው የሚለው የሚገባ አይመስለንም።
http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&task=view&id=25158&Itemid=52  እዚህ ይጫኑ። ካስቸገረወ press control key and double click it

ግለሰቦች ቴሌፎን እየደወሉ እኛ ከደሙ ንጹህ ነን ላሉት ይህን ከዚህ በታች ላለው የሸራተን ስብሰባ ትብብር ነው ወይንስ ካለማወቅ በአስራ ሀንደኛው ሰአት በስህተት ነው፧ ለሁሉም በሰፊው ስለምንመለስበት ለዛሬው በዋልታ የሕ.ወ.ሐ.ት የዜና አውታር በሆነው ድሕረ ገጽ የተለጠፈውን ይህን የሸራተን አዲስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስብሰባ እዚህ ለጥፈናል። ጉዳዩ መላ በውጭ አለም ለሚኖር ኢትዮጵያዊ በሙሉ ስለሆነ ከጀርባ ማስረጃ ጋር እስኪቀርብ ሆኖም ባካባቢ ለምትኖሩ ለጊዜው የመጀመሪያውን የቪዲዮ የውይይት ምስል ብትከፍቱ የግሰቡ ሐሳብን ለመረዳት ይቻላችኋል።


No comments:

Post a Comment