Wednesday, September 29, 2010

እነሱም እኛን ይላሉ፤ እኛም እነሱን እንላለን።

ፖለቲካና ፖለቲከኞች ሲሉና፣ ስንል
ᎀኤል ሽፈራው/ዳላስ

ለውይይት ይሆነን ዘንድ ይህን የተለመደ አባባል አቅርበናል። ይህ ቃል ባገራችን በብዙ የተለመደው ለሰበአዊ መብት፣ ለዴሞክራሲ፣ ለማነኛውም አይነት እኩልነት ሲሉ ለሚሟገቱ ሁሉ የሚሰጥ ቃል ነው። ብዙሐን ዜጋ ፖለቲካ የሚለውን ጥሬ ቃል ጨርሶ አይጠቀምበትም፣ ወይንም አያውቀውም። አወቅን የሚሉት ቃሉን በአግባቡ አይጠቀሙበትም። በይበልጥም ባገራችን ላለፉት 40 አመታት በተደረገው የሰበአዊ  መብትን፣ እኩልነትን፣ ዴሞክራሲን የማስፈን ትግልና በአንባገነን መንግስቶች የተደረገው ጭፍጨፋ የሕዝብ ልጆችን የበላ በመሆኑ ፖለቲካን ከዚህ የመብት ማስከበር ትግል ጋር በማያያዝ፤ ሰው በላ ጭራቅ አርገው ያቀርቡታል። ይህን የተገነዘቡት አንባገነኖች ግዛትና ስልጣን ለተወሰነ ክፍል የተሰጠ ሌላው ዜጋ ለጥ ሰጥ ብሎ የሚገዛ መሆኑን ለማሳየት የቃሉን አገባብ ለሚቀናቀኗቸው መጠቀሚያ እንዲሆን ይገለገሉበታል። ዛሬ ፖለቲከኛ የሚለው ቃል በስልጣን ላይ ላሉ ጨቋኝ ገዥወች የሚጠቅም ሳይሆን። ለፍትህ፣ ለዴሞክራሲና ለሰበአዊ መብት መከበር ለሚታገሉ ሐይሎች የሚሰጥ ማስፈራሪያ ቃል ሆኗል።

ለመሆኑ ፖለቲካ ማለት ምን ማለት ነው? ቀጥተኛ ቃሉ እንደሚያመለክተው ሕብረተሰብን ሕግንና ደንብን አውጥቶ የሚያገለግል ማለት ነው። ፖለቲካ ስንል ሁሉም በህብረተሰብ ውስጥ ያለ። ከእለት ጉርስና ልብስ ጀምሮ እስከ ማሕከላዊ አስተዳደር ያለው ማለት ነው። ፖለቲካ እንደየአገዛዞች ይለያያል። ከኛ አገር አንባገነኖች በፈረቃ ከሚገለገሉበት አዛዥ፣ ናዛዥ የሆነው ፖለቲካና፤ ዜጎቻቸው በአንድ ማህከላዊ ስርአትና ደንብ ለማንም በማያዳላ ሕገመንግስት ሕዝብ በሚመርጠው የሚተዳደሩ አገራት፤ ያለው ፖለቲካ የሰማይና የምድር ያክል ልዩ ናቸው።ከቃሉ በስተቀር በአፈጻጸምና ተግባራት የሚያገናኛቸው የጋራ የሆነ ምንም ነገር የላቸውም። ፖለቲካ ስሙ አንድ ይሁን እንጅ ከላይ እንደጠቀስነው በሁሉም የህብረተሰብ ክንዋኔወች ስለሚገባ ለምሳሌ፤ የቤተክርስቲያን ፖለቲካ፣ የኮሚውኒቲ ፖለቲካ፣ የዩኒየን ፖለቲካ ወዘተ እያሉ ይጠቀሙበታል። ፖለቲካ በእንዲህ አይነት ትርጓሜው በየስብስቡ ውስጥ ሰወች ሕግና ደንብ አውጥተው የሚተዳደሩበት ማለት መሆኑ ነው። ይህን ወደኛ አገር ብናዞረው። የእድር ፖለቲካ፣ የእቁብ ፖለቲካ፣ የሰንበቴ ፖለቲካ፣ እልፍ ብሎም የብሎግ ፖለቲካ ብንለውም ይቻላል ማለት ነው።

አንዳንድ ጠበብቶች ከምንበላውና ከምንጠጣው ጀምሮ ማነኛውም ነገር ፖለቲካ ተጨምሮበታል ይላሉ። ይህ አበባል በእርግጥም ትክክል ነው። የዩ ኤስ አሜሪካ libertarian አስተሳሰብ ያላቸው ስብስቦችም ሆነ ግለሰቦች ከለዘብተኛ liberal አስተሳሰብ ካላቸው የሚለያቸው አንዱና ዋነኛው ነገር። ለዘብተኞች ሁሉም ነገር ደንብና ድንጋጌ ሊኖረው ይገባል ሲሎ ሊብረተሪያኖቹ ምንም አይነት ድንጋጌ አያስፈልግም ይላሉ። በሁለቱ መካከል ያለው የአስተሳሰብ ልዩነት መንግስት ይኑር በሚልና መንግስት አይኑር በሚሉት (anarchist) መካከል ካለው በትቂት ቢለይ ነው። ሆኖም ሁለቱም አይነት አስተሳሰቦች ፖእለቲካ ናቸው።

አንዳንድ ወገኖች ሁሉን ነገር ፖለቲካ ነው ሲሉ ይደመጣል አበባሉ ትክክል ሆኖ ሳለ ፖለቲካ ማለት እነሱን የማይጨምር አርገው ይወስዱታል። ሌሎች ደግሞ ፖለቲካ አንወድም ሲሉ ይደመጣሉ። ይህ አባባል በየትኛውም ትርጓሜ ቢሆን ስህተት ይሆናል። ፖለቲካ ማለት ከምንለብሰውና ከምንመገበው ጀምሮ ያለ ነገር ነው ካልን። ፖለቲካና ኤሌክትሪክ በሩቅ፤ ፖለቲካ እንጠላለን የሚሉትን አላወቃችሁም ብንል አልተሰሳትንም ማለት ነው። ምክንያቱም ማንም ሰው ከፖለቲካዊ ድንጋጌወች ውጭ እራሱን ነጻ አድርጎ አያውቅምና። ማነኛውም የእለት ከለት ኑሮና ክንዋኔ ፖለቲካዊ ይዞታ ካለው እንደወፍ ነጻ ነኝ ካልተባለ፤ ከፖለቲካ የራቅን አይደለንም ማለት ነው። በመሰረቱ ፖለቲካ አልወድም፣ ወይንም ፖለቲካና ኤሌትሪክ በሩቅ ማለትም እራሱን የቻለ ፖለቲካ ነው። እንደስብስብ፣ ወይም እንደማሕረሰብ አንዱን ወገን ሌላው እጠላለሁ ማለት ፖለቲካዊ ውሳኔ ነው። አንድ አይሪሽ እንግሊዛዊውን እጠላለሁ እንደማለት ይቆጠራል። ወይንም በኛ አገር ወያኔ እንዳመጣብን ትምክህተኛ፣ ነፍጠኛ እንደሚሉት ቃላት ማለት ነው። እነዚህ ቃላት ውስጠ ሚስጥር አላቸው። አንድ ጥቅል ማሕበረሰብን በጅምላ ትምክህተኛ፣ ነፍጠኛ ይሉታል። ይህም የጥላቻ ፖለቲካ ይባላል ማለት ነው። ለመሆኑ የፍቅር ፖለቲካ አለ የሚል ጥያቄ እንዳይነሳ እንጅ የሚሆነው መልስ ሁሉም ነገር ይሁን ከተባለ ፖለቲካ ነው ማለት ነዋ።

እዚህ በአሜሪካን አገር እንደምንታዘበው፤ ለምሳሌ ውርጃን የሚቃወሙና የሚደግፉ ሰወች አሉ። ለነገሩ እራሴን አንዱ ባደርግ ከዚህ ውስጥ የሚሰማኝን መናገር እችላለሁ (prochoice,. prolife) ይባላሉ። ሁለቱ ክፍሎች የሰማይና የምድርን ያክል የተራራቀ አመለካከት አላቸው። ታዲያ (abortion) የምትለዋን ቃል ሁለቱም አይጠቀሙባትም። ሁለቱ ቃሎች ወደ አሜሪካ የሕግ ዙሪያም ሆነ በሁለቱ ተቀናቃኝ ፓርቲወች ሚና ለይተው በየምርጫው እንደመስፈርት ለሕዝቡ ይቀርባሉ። የእምነት ቤቶች ሳይቀር ተመሳሳይ የሆነ አፈራረጅ አላቸው። (the Christian right movement) የሚባለው የወግ አጥባቂውን ፖለቲካዊ መስመር የሚያራምድ ሲሆን ለዘብተኛ የሆኑ አቢያተ ክርስቲያናትም አሉባቸው። Interfaith dialog, የተለያዩ አማንያንን በአንድ ማህከል ለማስቀመጥና በእምነቶች ተማካኝቶ በየጊዜው የሚነሱ ግጭቶችን ለማስቆም የሚጥሩ፤ መተዋወቅንና መግባባትን እንዲመጣ የሚደክሙ ክፍሎችም አሉበት። ታዲያ እነዚህን መሰል የሐይማኖት ተቋማት ፈጽሞ የማይገናኙ የእምነት ጎራወች ናቸው ማለት ነው። በየሁለት አመቱ ለህግ መወሰኛው ምክር ቤት ምርጫም ሆነ በየአራት አመቱ አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ከላይ የጠቀስናቸው የእምነት ጎራወች ሚና ለይተው በሁለቱ የፖለቲካ ጎራወች ተቧድነው የምረጡን ዘመቻውን በየፊናቸው ያደርጋሉ።

ዛሬ አለምን የሚያምሳት በሐይማኖት ዙሪያ ተሳቦ አንዱ በሌላው ላይ የበላይ ለመሆን። ወይንም ግዛትና ስልጣን ይገባኛል የሚልና፤ አይሆንም በማለት የያዘውን የበላይነት ላለማጣት በሚፍጨረጨረው መካከል የሚደረገው ጦርነት ነው። ላለፉት 70 አመታት በፍልስጤማውያንና በይሁዳውያን መካከል የተደረገው ጦርነት ከዚህ የተለየ አይደለም። ፍልስጤሞችና ይሁዲወች የአንድ ዘር ትውልዶች ሆነው ሳለ የሚለያቸው ሀይማኖቱ ነው። አብሮ ላለመኖርም ይህን ያክል ለገላጋይ አስቸጋሪ የሆነው ግጭታቸው ሐይማኖታዊ ነው ይባላል። ሆኖም ውስጠ ሚስጥሩ አንዱ በሌላው የበላይ ሆኖ ለመግዛት ፖለቲካዊ ፍላጎት ነው። መፍትሄውም አማንያኑ ሐይማኖታቸውን መቀየር ወይንም አንድ ሌላውን ማጥፋት ሳይሆን። ፖለቲካዊ የሆነ መፍትሔ የማግኘት ነው።

ወያኔወች ከ35 አመት በፊት ተደራጅተው ኢትዮጵያ የምትባል አገር ነፍጠኛ ትምክህተኛ ሰራሽ የመቶ አመት ታሪክ ያላት፤ እሷን ከፋፍለን በቦታዋ የብሔር በሔረሰቦችና ሕዝቦች ፌደሬሽን እንፈጥራልን ማለታቸው። እንደሚሉት አንድ ቋንቋ ተናጋሪ ጨቋኝ ሌሎች ተጨቋኝ ሆነው አልነበረም። ወይንም ንጹህ በደም ያልተደባለቀ ትግሬ፣ አማራ፣ ኦሮሞ ወይንም ከሌሎች ኖሮ አይደለም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔወችም ሆኑ ሌሎች ክልልተኞች እንደሚሉት ሳይሆን የተገላቢጦሽ፤ አንዱ ከሌላው የተዋለደ፣ ለብዙ ሽህወች አመታት አብሮ የኖረ ነው። ታዲያ እነሱ የበላይ ሆነው ለመግዛት ሲፈልጉ አቋራጩ መንገድ፣ በቀላሉ ለመቀስቀሻ የሚጠቅም ሆኖ በመገኘቱ ተጠቀሙበት። የኢትዮጵያ ሕዝብ በማለት ፈንታ፤ ኢትዮጵያ ከተለያዩ አገሮች ተውጣጣ እንደተሰራች ሁሉ (የኢትዮጵያ ሕዝቦች ይላሉ) በእጅጉ የከፋው ደግሞ ከፋፍሎ መግዛትን ይሁነኝ ብለው መቀጠላቸው ነው። ይህ ማለት እንግዲህ ወያኔወችም ሆኑ ሌሎች ጎጠኛ አስተሳሰብ ያላቸው፡ ለኔነው ለሚሉት ከልብ ተቆርቁረው ሳይሆን። የተሻለ ቀለል ያለ አማራጭ ነው ብለው ስላመኑና የፖለቲካ የበላይነቱን በከፋፍለህ ግዛው እረጅም የግዛት ዘመን እናገኛለን በማለት ነው። ይህም ፖለቲካ ነው እንዴውም የከፋ የከረፋ ፖለቲካ።

Saturday, September 25, 2010

History is not melodrama, even if it usually reads like that. Robert Penn Warren

89 በኬንያ ፍርድ ቤት ቀርበው የይመለሱ ፍርድ ተፈረደባቸው
ኤል ሽፈራው/ዳላስ

አገራቸውን ለቀው ለአመታት በስደት ይኖሩ የነበሩ የኢትዮጵያ ስደተኞች ከኬንያ እንዲወጡ ተፈረደባቸው። በተመሳሳይ ዜና 26 የመንን አቋርጠው ወደ ሳውዲት አረብ ሲሰደዱ በየመን ወታደሮች ተይዘው ያለፍርድቤት ትእዛዝ ወዳገራቸው እንዲመለሱ የየመን የድንበርና የኢሚግሬሽን ሚኒስቴር አስታወቀ። ይህን ዜና አዲስ ነው ብለን ሳይሆን የኢትዮጵያውያን መከራ ዛሬ ያለም ዙሪያ የእለት ጉዳይ መሆኑን ለመጠቆም ነው።

ለአለፉት አስር አመታት በአረብ አገሮች የተሻለ ሕይወት ለማግኘት የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ወጣት ሴቶች እየደረሰባቸው ያለው ጭቆና ከልክ ያለፈና ጭካኔ የተሞላበት ነው። አንዳንዶቹ የአካል ጉዳት ከደረሰባቸው በኋላ፤ የመኖሪያ ፈቃዳቸውን ጉዳቱን አድራሽ ቀጣሪወቻቸው በመቀማት መልሰው እስር ቤት እንዲሄዱ ያደርጓቸዋል። ይህ ያገር ውርደት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን የአለም የሰባዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተደጋጋሚ አቅረበዋል።

ዛሬ ከሁሉም ያሳዘነንና ግፉ የእጥፍ ድርብ እንዲሆን ያስገረመን የኬንያ መንግስት በስደተኛ ኢትዮጵያውያን ላይ ያስፈረደው ሕገወጥ ፍርድ ነው።

ኢትዮጵያ ለኬንያም ሆነ ለመላ አፍሪካ አለኝታ በመሆን ለዘመናት በአውሮፓ የቅኝ ግዛት ስር ሲማቅቁ ለነበሩ ሁሉ በቀጥታ በትግላቸው ተሳታፊ በመሆን ለነጻነት ለተደረገው ተጋድሎ በደጀንነት ብሎም በቀጥታ ተሳታፊነት አግዛለች። በተለየም በጆሞ ኬንያታ የተመራው (Mau Mau) የነፃ አውጭ ድርጅት በኢትዮጵያ መንግስትና ሕዝብ የተደረገለት ትብብር ያሁኖቹ ገዥወች ቢረሱት ታሪክ ሊዘነጋው አይችልም። ኬንያታ በእንግሊዝ ፍርድቤት 1953 .. የሰባት አመት ጽኑ እስራት ፍርድ ሲፈረድባቸው በዚያን ጊዜ የነፃዋ አገር መሪና በውጭም ከፍተኛ ዝና የነበራቸው ቀዳማዊ ሐይለስላሴ ወዳጅ ለነበረው የእንግሊዝ መንግስት ቅሬታቸውን ገልጸዋል። በዚያ ብቻ አይደለም የተነሳሳው አመጽ እንዲፋጠን ቁሳዊና ሎጅስቲካዊ ድጋፍ አበርክተዋል። ውጤቱም 1958 .. ኬንያታ ከእስር ተፈተው በአንድ ከተማ ተወስነው ከእንግሊዝ መንግስት ጋር የተደረገውን ድርድር በመሪነት አካሂደዋል። ከነፃነት በኋላ በነፃዋ ኬንያ ሊያገለግል የሚችል ሕገመንግስት በማርቀቅ በግዞት ቤታቸው ተወስነው ስራቸውን ጨርሰዋል። ለዚህ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስት ከጎናቸው መቆም ዋና ሐይል እንደነበር ታሪክ ይዘክረዋል።

ለአፍታ ለዝክረ ታሪክ ይሆነን ዘንድ፤ በሱዳን ደቡብና ሰሜን ሱዳን መካከል ተነስቶ ለእልቂት የተቃረበውን የእርስ በእርስ ጦርነት በማቆም። በናይጀሪያ የብያፍራ አመጽ የመጨረሻ እልባት ያገኝ ዘንድ በመሐል በመግባት፤ በሁለቱም አገሮች የነበረውን የመገንጠል አደጋ በሰላም በመፍታት አንድነታቸውን እንዲጠብቁ መፍትሄ በመስጠት። በአልጀሪያና በሞሮኮ ተነስቶ የነበረውን የድንበር ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲያገኝ በማድረግ። በደቡባዊው አፍሪካ የነበሩት የነፃነት ትግሎች በቀጥታ ተሳታፊነትና በአሰልጣኝነት፤ ኢትዮጵያ ያላበረከተችው ድጋፍ አልነበረም። አፍሪካውያን ነፃ በወጡበት አፍላ አመታት 1958 .. በአክራ ስብሰባ ኢትዮጵያ ነጻ የትምህርት እድል ለወጣት አፍሪካውያን በመስጠት ሰፊ አስተዋጽኦ ተደርጓል። ያሁሉ ተረስቶ አገራችን የባሕር በሯን ስትነጠቅና በሁለት ጎጠኛ ወንድማማቾች አደጋ ሲደርስባት ብሎም ዛሬም ኢትዮጵያውያን በመቶ ሺሆች የስደት ኑሮ ሲባዝኑ፤ አይዟችሁ ብሎ የደረሰላቸው አለመኖር እጅ አመዳፋሽ እንዲሊ ሆኗል። ይባስ ብሎ የናት ጡት ነካሽ እንዲሉ በክፉ ቀን መጠጊአያ ፈልገው የተጠጉ ወገኖቻችንን ኬንያ መልሳ ለወያኔ መንግስ ማስረከቧ (ይህ የመጀመሪያ አይደለም) የሚያሳዝን ድርጊት መሆኑን ልናልፈው አንችልም።

ምንጭ፤

Marina de Regt, Ph.D, Amsterdam School for Social science Research
University of Amsterdam

History 101, Spring 1999, Professor Maiershofer

Wednesday, September 22, 2010

You can't depend on your eyes when your imagination is out of focus, Mark Twain

ግራ ቀኝ ያለማየት ችግር፤ የሚያስከትለው ጉዳት
ᎀኤል ሽፈራው/ዳላስ

መረዋ በተባለ ብሎግ የሚያስነብበን መልካም ጽሁፎች እንደተጠበቁ ሆነው። ጸሐፊውም ሆነ ባልደረቦቻቸው ለሁሉም አይነት የህብረተሰብ ክፍል ያላቸውን ጥላቻ የሚያንጸባርቁ መጣጥፎች ያለማቋረጥ ማቅረቡ ውብና ለዛ ሊኖረው የሚችለውን አበርክⶆአቸውን ሊያደበዝዝ ይችላል። ስለመብት እየተናገሩ የሌሎችን መደራጀት፣ መቃወም አልያም ማጣጣል፤ ይሁነኝ ብለው የተቃዋሚወችን ማናናቅ፤ አንድየ የሆነውን የእምነት ቤት ፍርድቤት አቅርቦ የመብት ማስከበር ትግል ነው ብሎ መፈጸም፤ ጉዞው ወዴት እንደሁ ለምናውቅ ብዙም አይደንቀንም።

ይህ ብሎግ በአንድ ነገር ላይ ብቻ አተኩሮ የቸከ ተደጋጋሚ እሰጥ አገባ ውስጥ ለመግባት ፍላጎቱም ሆነ እምነቱ አይደለም። የሐይማኖት ስራትን የሚያውቁ ሊቃውንት በጉዳዩ ቢሳተፉም የሚሻል እንደሆነም በጥብቅ እናምናለን። ተቋሙ መበደሉን እያየን ገለልተኛ ለመሆን በፍጹ አይቻለንም። ይህን የእምነት ቤት ለመስራት የእስልምና ተከታይ ወገኖቻችን ሳይቀር ተሳትፈዋልና። የሆነው ሆኖ ግን የማይሆን ነገር ስናይ በዝምታ ልናል አይቻለንም። ቅዳሜ ሴብተምበር 18/2010 በመረዋ ብሎግ ጸሐፊ የተንጸባረቀውን ለመመልከት እና መስመር እንዲይዝ ለመጠየቅ ተገድእናል።

ግለሰቡ የከሳሽን ወገን እንደ ተበዳይ፣ መብቱን እንደተነፈገ አድርገው ለማቅረብ በተደጋጋሚ በሚወጡ መጣጥፎች በዝምታ የሚከታተለውን ወገን ለማስጨበጥ ሞክረዋል። ሌላው “ልጅ ለናቷ ምጥ አስተማረች” እንዲሉ ተሰደብን የሚለውን ቃል በተደጋጋሚ ያነሱታል። እዚህ ላይ ማንም እንዲገነዘብ የምንፈልገው ጉዳይ ይህ ጸሐፊም ሆነ ብሎጉ፤ ወገንን ከማንቋሸሽ ውጤት፣ ስምምነት ይፈጠራል። ወይንም መልካም ነገር ይፈጠራል ብለን አናምንም። ካልተሰሳትን መረዋ ሲጀምር የስድብ ውርጅብኝ በአንድ ቤተሰብ ላይ እንዳወረደ ግን መዘንጋት አይቻልም። ይህ አሁንም ለግንዛቤ እንዲቀመጥ ያስፈልጋል። የሆነው ሆኖ ያም ጸያፍነቱ ታውቆ አሁን በተያዘው መልክ ለመቀጠል የቁርጥ እምነት ከሆነ እሰየው እንላለን። ሆኖም በድጋሜ ለግንዛቤ ሆነ ለመተዛዘብ እንዲሆን በዶክተር ግርማና በቤተሰብ የወረደውን የስድብ ውርጅብኝ ዘሎ እራስን ከዚያ ንጹህ ነን ለማለት መሞከሩ አግባብ የለውም እያልን። ብሎጉ በያዘው እንዲቀጥል አበጀህ እንላለን። ከላይ የጠቀስሁትን ተግባር ዳግም ላለመመለስ ለራስ ማሐላ ገብቶ ለክርክርም፣ ለውይይትም መቀጠሉ አንድ እርምጃ ነው።

በስነ ጽሁፍም ሆነ በትችት አለም። ማንም ተች ወይም ጽሁፍ አቅራቢ ወይንም ተከራካሪ በያዘው አጀንዳ ላይ አስቀድሞ ስለሚጽፈው ጉዳይ እውነትነት ሊያስጨብጥ ይገባል።፡ይህ እውነትነት የሚገኘው እመኑኝ ወይም በምሐላና በመገዘት ሳይሆን የጽሁፉ፣ ትችቱ፣አለያም መከራከሪያው ምንጭ ሲኖረውና በማንም አንባቢ ሊገናዘብ የሚያስችል ማመሳከሪያ ሲቀርብ ነው። አለበለዚያ ድሮ እንደምናውቀው ተራ ፕሮፓጋንዳ ወይንም ያው ዞሮ ስድብ ከመሆን አይዘልም። ለምሳሌ የዚህ ጽሁፍ አቅራቢ በመረዋ በኩል ፖለቲካዊ ግፊት አለ ብሎ ያምናል። ይህንም በማስረጃ ለማቅረብ ይቻለዋል። በአቶ ሙሌ ታረቀኝ ከአኢትዮጵያ የወያኔ ኤምባሲ ዲሲ የመጣ ሰው በጠራው የአማራ ልማት ማሕበር (አ.ል.ማ) በተባለ ስብሰባ ቅዳሜ ኤፕሪል 24/2010 በዳላስ መደረጉን “በትኩረት ፮” ኢትዮሚዲያና በሌሎች ድሕረ ገጾች በወጣ ሪፖርታዥ መረዳት ችለናል። በዚያ ስብሰባ ላይ ያሁኖቹ ቤተክርስቲያኑን ፍርድ ቤት አቅራቢወች ተገኝተው የሚገባ ድርሻቸውን በሀሳብም በቁሳቁስም አበርክተዋል። ይህ ስብሰባ በተካሄደ ሳምንት እሁድ ሜይ 2/2010 በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቅድመዝግጅት የተደረገበት፣ በእርግጥም የቪዲዮ ቀራጮች ተዘጋጅተው ሁላችንም እንደታዘብነው በ ቻናል 4 የምሽት ዜና ሆኖ የቀረበውን ገመና ገላጭ የሆነውን ምስል በሁካታው ሲቀረጽ እንደነበር ሁሉም ያውቃል። ይህ ከላይ የጠቀስነው እንደተጠበቀ ሆኖ የዚህ የመረዋ ብሎግ ጸሐፊ ደጋግመው ስለፖለቲካ በተለየም በውጭ የመለስን/ወያኔ አስተዳደር ይቃወማሉ በሚሉት ተቃዋሚ ለማላከክ መከራቸውን ሲያዩ ታዝበናል። የራስ ስራና ተግባርን ለሌሎች ለምን መስጠት አስፈለገ፧ ጥያቄአችን ነው። እንደእውነት ከሆነ የዚያ ብሎግ ጸሐፊ መንግስትን በሲቃ ይደግፋሉ። ይህም መብት ነውና ባልከፋ። ለምን ተናገራችሁብኝ ብለው ይጨነቃሉ። ይህም ሰው የሚወደውን፣ የሚጨነቅ፣ የሚጠበብለትን አትንኩ ማለቱ ነውርነት የለውም። ሆኖም ዞረው ተመልሰው የሚወዱትን እቃ (ወያኔን) ተናገሩት በሚሉት ወገኖች ላይ ያላግባብ የቃላት ክስ ያቀርባሉ። ደግነቱ የመናገር ነጻነት ያለበት አገር መሆኑ። ከሳሽ በተከሳሽ ላይ ማስረጃ ማቅረብ የሚገደድበትም ህገመንግስታዊ አገር በመኖራችን እንጅ። አገርቤት ሆነን ቢሆን (በአ.ል.ማ) በኩል ይቃወማሉ በተባሉት ወገኖች ላይ እንደወንድማችን አካሄድና አረማመድ ቢሆን ከትልቁ ይሙት በቃ ፍርድ ለማሳነስ የግምት መዛባት ይሆን ነበር። ጸሀፊው በሰሞኑ በቁጥር ፵፫ መጣጥፍ እርስ በራሱ የሚጋጭ ሀሳቦችን አስነብበውናል።

በሜይ ፪ ቀን እሁድ ከቅዳሴ በኋላ ስለነበረው ሁከት አስመልክተው ቤተክርስቲያን ፖሊስ እንዴት ሊመጣ ተፈቀደ በሚል ከዚህ በታች ያለውን ይላሉ።

ታዲያ በአሁኑ ሰዓት በአንድ ወገን  በጥቂት የቤተክርስቲያን አመራር ክፍልና በጣት በሚቆጠሩ ደጋፊዋቻቸው በአንጻሩ መብታችንን አናስደፍርም በካህን ታጅበን እንጂ በፖሊስ ተከበን አናመልክም በሚሉ ምእመናን መካከል የተጀመረውን መተናነቅ ስናስተውል  እውነትም ፈተናው አስከፊ እንደሆነ ታየን።
ከላይ በተጠቀሰው አባባል። ብዙ ደካማ እናቶችና አባቶች፤ ሕጻናትን ጨምሮ ባሉበት ቦታ ስርአት አልባ ግርግር ቢነሳና ጉዳት ቢደርስ ማን ተጠያቂ ሊሆን ይችላል፧ የሚለውን ብንዘል። ለምንስ ጉዳት እስኪደርስ ይጠበቃል የሚሉ ወገኖችን ሐሳብስ እንዴት ድጦና አሳንሶ ማየት ይቻላል። የጸሐፊውን አባባል ሙሉ በሙሉ እጋራለሁ ልበል ምክንያቱም እኛው በእኛ መፍታት የሚቻለውን ለምን ከውጭ ሐይል አመጡ የሚለውን አባባል ማለት ነው። ሆኖም እንዳየነው የተነሳው ሁካታ ቢቀጥልና ገላጋይ የጸጥታ ክፍል ባይኖር አማራጩ ምን ሊሆን ይችል ነበር ብሎ መጠየቅ የሚገባ ይመስለኛል። የዚህ ጽሁፍ አቅራቢ የቤተክርስቲያኑን አስተዳደር ከመተችቱ በፊት የነበረውን ሁናቴ ለምን ብሎ ጠይቆ መልስ ተሰጥቶት ሁለት ሰአት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ተግባሩን በተጨባጭ ተመልክቷልና። በአንጻሩ የመረዋው ትችት አቅራቢ በጊአዜ በማናውቀው ጉዳይ ይህ ድርጊት ሲፈጠርም ሆነ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ከጸሎት በኋላ በነበረው ግርግር ከውጭ ቆመው እንደነበር ግን እራሳቸውም ቢሆን ሀሰት እንደማይሉ እገምታለሁ።

መብታችንን አናስደፍረም በሚሉ ምእመናን እና በትቂት የቤተክርስቲያን ደጋፊወች መካከከል የሚለው ይህ በዚህ ጸሐፊ በተሰመረበት ቃል ለአፍታ እንተች። የመረዋው ትችት እንበለው ክስ፣ አቅራቢ። መብት የምትለዋን ቃል ደጋግመው ይጠቀሙባታልና ትርጉሙ ከቤተክርስቲያኑ ጋር እንዴት እንደሚታይ ስላልገባን ለመጠየቅ ተገደናል። ምናልባት ይህን በሚቀጥለው መጣጥፋቸው ያቀርቡታል ብለንም እንገምታለን። ሆኖም እንደሚታወቀው ቅዱስ ሚካኤል ከተከፈተ ከ24 አመታት በላይ ነው። በዚህ ባሳለፍናቸው አመታት ሁሉ በስህተትም ይሁን ተዘሎ በግል የተዳደረበት ወይም ያለ አባላት ፈቃድ ግለሰብ የቤተክርስቲያኑን ደንብ ተላልፎ እኔብቻ ያለበት ጊዜ የለም። አባላት መርጠው ያስቀመጧቸው የቦርድ አባላት በፈረቃ አገልግሎት ሰጠዋል። አሁንም በተመሳሳይ የመታዳደሪያ ደንቡን በተደገፈ ተመርጠው የሚያስተዳደሩ ወገኖች አሉ። እነዚህ አደረጉ የሚባለውን ከህግና ደንባችን ውጭ የሰሩትን ማቅረብ ተገቢ ሆኖ ሳለ የወያኔው መለስ “የአይን ቅንድባቸው ካላማረንም እናባርራለን” እንዳለው። እኔና ጓደኞቸ ስለማንወዳቸው፣ ወይንም አቡነ ጳውሎስን ስላልተቀበሉልን፣ ወይንም በሕግና ደንብ ተመርኩዘው ስለቆሙ። የኛን መብት ተጋፍተዋል ካልሆነ። መብታችን የሚባለውን ቃላት በተግባር ቢያሳዩን ተባባሪ በሆንና አብረን በጮህን መልካም ነው እንላለን። ሌላው ለግንዛቤ ያክል፤ አንባ ገነንነት እስከምናውቀው ባገራችን በወያኔው መለስና በሹመኞች በአባ ጳውሎስ እንጅ በየጊዜው በሚመረጥ ቦርድ ይኖራል ለማለት፣ ለዚያም ማገናዘቢያ ለማቅረብ ትንሽ የሚከብድ ቃል ይመስለናል። “ቃል” ያልነው በተግባር ከጥላቻ ያልዘለለ እውነትነት የሌለው ክስ ለማለት ነው።

ከላይ የመረዋው ጸሐፊ ቦርዱ ለምን ፖሊስ አመጣ ብለው እንዳልተከራከሩ ወይም እንዳልጻፉ ወረድ ብለው እንዲህ ይሉናል

እኛ ይህንን ገምግመን መስቀል ካልገዛው ሕግ ይዳኘው ብለው የተነሱትን ደግፈናል።
አንባብያን ግንዛቤ እንዲያገኙ እስኪ ለምን ፖሊስ ጠሩ ብሎ መመጻደቅና አንድ ክስ ሳይዘጋ በእምነት ቤት ያውም በጋራ የገዛነው። በህግና ደንብ በሚተዳደር። የውስጥ መተዳደሪያ ባለው። በየጊዜው የሚፈራረቁ ተመራጭ አስተዳዳሪወች ባሉበት ቤት ለምን ብለው ለሁለተኛ ክስ እንደሄዱ ግን በትክክል ገልጸውት አያውቁም። በዚህ ጸሀፊ እምነት፤ የጋራ የእምነት ቤትን መክሰስ አግባብ ያልሆነ አፍራሽ ተግባር ብሎ ያምናል። የፖሊስ መምጣትን የተቃወመ ሳይውል ሳያድር ፍርድቤት ሄዶ መጥሪያ ይዞ ሲመጣ ስናይ አዝነናል። እንደወያኔው መሪ እሳቸውም ቅንድባቸው የማያምር የሚጠሏቸው ቢኖሩ አንድም ከማያዩበት መሄድ አልያም እንዲለቁላቸው ግለሰቦችን መጠየቅ ከፍርድ ቤት ጉዞ በእጅጉ የተሻለ ነው የሚል እምነት የዚህ ጸሀፊ አቋም ነው።

ፖሊስ አመጡብን ብሎ አናውሮ የተናገረ ጸሀፊ፡ በዚያ ገጽ እኛም ፍርድቤት ሄድን ማለት ትርጉሙ አይገባንም። ወይም በአንድ ስብእና ሁለት የሰውነት ባሕርይ ካልሆነ።

የኛ ችግር በመብት እረገጣ ላይ ነውና ለዚህ ደግሞ ከሕግ ውጭ መፍትሄ ይኖራል ብለን አናምንም።
ይህ አበባል ግልጽ ነው። ቅዱስ ሚካኤል ከሩሲያውያን ደባልነት ወጥተን ኪንግ መንገድ ላይ የነበረውን ስንገዛ። በቅድሚያ ለዚያ ያደረሱን ገለሰቦች እንደነ አቶ ኪዳኔ ምስክር፣ እቶ ሰይፉ ይገዙ ጊዜና ገንዘባቸውን ለግሰው ለዚህ ያበቁን ምስጋና ይድረሳቸውና። እንዲሁም ያለመታከት በአንድ ሆብሎ የቆመው ምእመናንና ሌሎች ስማቸውን ያልጠቀስን ወገኖች ትብብር ለዘላለም ይኑር እያልን። ምናልባት የመረዋው ጸሐፊም አንዱ ሊሆኑ ይችላሉ። አላስታውስም። ከዚያ ጊዜ እስከአለንበት፤ ቤተክርስቲያናችን ፍርድቤት እስከቀረበበት ድረስ፤ ምንም ችግር አልነበረም ማለት አይቻልም። አለመግባባቶች ነበሩ። ሆኖም በውይይት የሚፈቱት በመልክ በመልኩ ቀርበው ሲያሻ ሽማግሌ አልያም ተወቃቅሶ እንደኖረ ግን ግልጽ ጉዳይ ነው። የፍርድቤት ነገር ከተጀመረ ወዲህ መፍትሄው እሱ ብቻ ብለው የቆሙ ምእመናን በማወቅ ወይንም ባለማወቅ እስካሁን እንዳሉ እናውቃለን። ያነን የመጀመሪያ ፍርድቤት ጉዳይ አገባደን ለሌላ ስንቀርብ ግን። ለምን የሚል ጥያቄ ማጫሩ አልቀረም። ይህን በአንድ በማያወላዳ ስንኝ ልዝጋው። ፍርድቤት መሔድ ዳግም ለማናችንም አያዋጣም። ፍርድቤት መሄድ ለሁላችንም በደል ነው። ማሕበራዊ ትሥስራችንን ያናጋል። ሰላምንና ፍቅርን ያርቃል። በቦታው ማንም ያሸንፍ የመጨረሻ ውጤቱ አንዱን አግላይ ነው ባይ ነን። አሁንም ዳግም ልንረዳው የተቸገርነው ምርጫ ባለበት ቤት የመብት መገፋት የሚለውን ቃል ነው። ይህን ቃል በመልኩ ቢያስረዱን ዳግም እንጠይቃለን። እስከፍርድቤት በምስክር ቃልነት የቀረበ በመሆኑ ማለት ነው።

ወረድ ብለው ጸሐፊው እንዲህ ይላሉ።

አገር ቤት ያልተሳካ ፖለቲካ ዳላስ ያለውን ምእመን በማመስ በለስ ሊቀናን ይችል ይሆናል ብሎ  ማለም ደግሞ በፖለቲካ አለመብሰል ይመስለናል።

ይህ የጸሐፊው አባባል ለሁሉም ችግራችን ማሰሪያ ነው ይላሉ አንዳንድ ወገኖች። ጸሐፊው ስለቦርድ አንባ ገነንነት (በየሁለት አመቱ ስለሚመረጥ አካል) እያወሩ የመጨረሻ ዋና የጽሁፋቸው ማሰሪያ ስንኝ ይህ ከላይ የተቀመጠው ነው። ምናልባት እሳቸው የሚደግፉት ክፍል አሁንም 99.6% አሸናፊ ነኝ ብሎ ስልጣኑን ከያዘና  ሀያ አመታት እየገደለ ተቃዋሚን እያሰረ ገዝቶም ስላልበቃው ፍጹም አንባ ገነንነቱን ድፍን ኢትዮጵያ መረጠኝ በማለት የመቶ አመት ስራውን ቀጥሏል። ያልተሳካ ብለው የሚሳለቁበት ነገር ይህ ሆኖ። ጉልበተኛ በሕዝባችን ጫንቃ ተቀምጦ አናሳወች ጠበንጃ አስካለን ማንም አይነካን እያሉ በሚፎክሩበት አገር በእርግጥም ጸሐፊው ያልተሳካ የሚሉት ስላቃቸው ይህ መሆኑ ነው። ፍርድቤት ለመሄዳቸው ውስጠ ሚስጥርም የሚያፈቅሩትን መንግስት ይቃወማሉ የሚሏቸው ወገኖችን ለማስወገድ። ወይን ከአይናቸው እንዲርቁ ለማድረግ የተረገዘ ተቃዋሚን አልይህ የማለት ጥላቻ ነው ይላሉ አንዳንድ የተማረሩ ወገኖች። እንደአገር ቤቱ እኛ የ አ.ል.ማ አባላት ያለምርጫ ካልያዝነው የሚል ውስጠ ሚስጥር ነው የሚሉም አልታጡም።

ለማጠቃለል፦ የሚቻል ከሆነ አንባ ገነንነት እንዴት በቤተክርስቲያን እንደተፈጠረ። በይበልጥም ተመርጠው የማስተዳደሩን ቦታ በሚይዙ ሊሰራ እንደቻለ ብናይ።

በይበልጥም እምነትን ከግል የማሕበራዊና ፖለቲካዊ ፍላጎት ጋር መጨመር አደጋ እንዳለው መገንዘብ።

ከይሆናልና ከጥርጣሬ ወጥተን ጭብጥ ያለው፤ በማስረጃ የተደገፈ ክንዋኔን ቢቀርብ።

ይጠሉኛል፣ ወይንም ይቃወሙኛል ብሎ ማሰብ ከወዲሁ የፍርሐትና ጥርጣሬ ግድግዳ መገድገድ ሲሆን፤ ለማነኛውም አይነት ስልጡን ውይይት መላወሻ ነስቶ አይንህ ላፈር የሚያሰኘውን የጥላቻ ጅረት ለመዝጋት ወደራስ መመልከት።

ከሁሉም በላይ ስለመንፈሳዊነት ከተነጋገርን፤ ከአንድ ወጥ ጎዳና ወጥተን ግራቀኝ እንድናይ እራስን መምከር። በማለት እንጨርሳለን። የነገ ሰው ይበለን።